ጸጋው የሚገኝበት ሕይወት የሚለወጥበት

የእግዚአብሔር ሕዝብ የተረሳ የተተወ በሚመስለው ጊዜ፣ እግዚአብሔር አቻ የሌለውና ታላቅ መሆኑን ለሕዝቡ በመግለጥ ለእነርሱ ያለውን ርህራሄና ግድ የሚለው አምላክ እና አባት መሆኑን በማሳየት ያጽናናል። ችግሮቻችን ከእግዚአብሔር ታላቅ ኃይል አይበልጥም፤ ፍርሃታችን እግዚአብሔር ለእኛ ካለው የእረኛነት እንክብካቤ ብርታት ይልቅ አይበረታም፤

ሕይወት እምነታችንን በሚያወዛግብበት ጊዜ፣ ኢየሱስ ወደ ሰራቸው ሥራዎቹ እንደገና እንድንመለከት፣ ቃሉን በጥንቃቄ እንድናዳምጥ፣ እና ከመንፈሳዊ መሰናክል ወይም ግድየለሽነት ይልቅ በትሕትና እና በእምነት ምላሽ እንድንሰጥ ይጠራናል። የምናየው እና የምንሰማው ነገር እምነታችንን ይቀርጻል። እምነታችን ደግሞ አኗኗራችንን ይቀርጻል። ከክርስቶስ የምንሰማው እውነት ደግሞ ለሌሎች የምንመሰክረው መልዕክት ይሆናል። 

ኢየሱስ ክርስቶስ “ወደ ፈተናም አታግባን፣ ከክፉ ሁሉ አድነን እንጂ” የሚለውን ጸሎት ሲያስተምረን ድካማችንን እንድንናዘዝ እያስተማረን ነው፣ ያለብንን የመንፈሳዊ ውጊያ፣ እንዲሁም በእግዚአብሔር ላይ ጥገኞች መሆናችን፣ አብ ከፈተና ከልሎ በታማኝነት ጸንተን እንድንገኝ እንዲጠብቀን የጠላታችን ተንኮል እንዳያገኘን እንዲታደገን የቀረበ ጸሎት ነው፤
 

ይምጡ ያግኙን

ክርስቶስ ማዕከል የሆነበት፣ ቅዱስ ቃሉ የሚሰበክበት፣ ቤተ ክርስቲያን በተልእኮ ያለችበት። Christ-centered. Bible-preaching. Community on mission